
አቶ በጋሻው ደሳለኝ በድምጽ ከተቀዳ እማኝ ማስረጃ ላይ በሶስቱ ቀናት ጉባኤ የሚቀጥሉትን መልዕክቶች አስተላልፏል (ወደፊት እንደ አስፈላጊነቱ የድምጽ ቅጅው ፖስት እናደርጋለን)፡፡ አሁንም ቢሆን የድፍረት ቃላቶች የእግዚአብሔር ስም በሚጠራበት ቦታ ላይ ላለመስማት አውደ ምህረት ፈቃጆች ለማን እንደምትፈቅዱ አስተውሉ፡፡
23/05/06 ዓ.ም
- ‹‹ቄስ መነኩሴ አትፈልጉ እራሳችሁ ፀልዩ፡፡››
- ‹‹እኛ ፀልየን ሁለት ህፃናት ከHIV/AIDS ነፃ ሆኑ፡፡››
- ‹‹ያለ ክርስቶስ ስም ፀሎት አያርግም፡፡››
- ‹‹ክርስቶስ ብቻ ሙሉ ስም ነው፡፡››
- ‹‹ክርስቶስን ብዙ መውደድ ነው እንጅ ብዙ መስገድ አያድንም፡፡››
24/05/06 ዓ.ም
- በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ይሁዳ ብር ሲያዩ የሚጎመጁ አገልጋዮች አሉ፡፡
- ‹‹አገልግዬ ወጣቶችን ከብዙ ነገር አስመልጫቸዋለሁ›፡፡››
- ‹‹ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ ነው ለሌላ ለማንም አትስጡ፡፡››
- ‹‹በነፃነት ለማምለክ መውጣት በክርስቶስ ስም ነው፡፡››
- ‹‹በትናንትናው የስብከት አገልግሎታችን አንዲት በሽፍቶች ተደብድባ ዓይኗ ጠፍቶ የነበረ እህታችንእኔ እያሰብኩዋት ስለነበር ጉባኤውም እያሰባት ስለነበር ጉባኤው ሲያልቅ ዓይኗ በራ፡፡››
25/05/06 ዓ.ም
- ‹‹በመዳን ህይወት ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ የሚይዘው ኢየሱስ ነው፡፡››
- ‹‹የመጣችሁ እንግዶች ካላችሁ እኛ የምንሰብከው ኢየሱስን እንደሆነ እወቁ፡፡››
No comments:
Post a Comment